Home » ESAT Daily News » የኢሳት የገንዘብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ዘመቻን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

የኢሳት የገንዘብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ዘመቻን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

ታህሳስ 8 ቀን 2004 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) ከህዳር እስከ ጥር ወር 2004 ዓ.ም ሊያደረግ የነበረውን
የገንዘብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ዘመቻ ከጥር እስከ መጋቢት ወር 2004 ዓ.ም ማስተላለፉን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ።

 

ባለፈው የጥቅምት ወር መጨረሻ የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) ከህዳር እስከ ጥር ወር 2004 ዓ.ም የገንዘብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ዘመቻ እንደሚያደርግ ባወጣው መግለጫ አስታውቆ ነበር። በህዳር ወር ለመጀመር የታሰበው ዘመቻ ከዝግጅቱ ጋር በተዛመዱ የተለያዩ  ቴክኒካዊ ምክንያቶች ሳቢያ ወደ ጥር ወር ለማስተላለፍ ተገዷል።

 

ከላይ በተጠቀሰው  የጥቅምቱ  መግለጫ ኢሳት በወቅቱ የነበረበትን ሁኔታ ገልፆ የነበረ ሲሆን፤ በዚህም፥ ኢሳት፤

  1. የአጭር ሞገድ የሬድዮ ስርጭት ፕሮግራም ሰኞ፣ እሮብና አርብ በ15390 kHz ማክሰኞ፣ ሃሙስ፣ ቅዳሜና እሁድ 15370 kHz ወደ ኢትዮጵያ በማሰተላለፍ ላይ መሆኑን፣
  2. እየጠነከረ የመጣውን የገዢውን ፓርቲ አፈና ይበልጥ ለመቋቋም የ24 ሰዓት የሳተላይት ሬድዮ ስርጭት በቀጥታ ወደ ኢትዮጵያ በሳተላይት ቴሌቪዥን ማሰራጨት መጀመሩን፣
  3. ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የሆነውን “አይፒቲቪ“(IPTV) በመጠቀም ውጭ ሃገር ለሚገኙ ኢትዮያውያን ስርጭቱን በስፋት ለማድረስ በቀጥታ በቤታቸው ቴሌቪዥን እንዲሁም በተንቀሳቃሽ ስልክ (MOBILE) ማየት የሚችሉበትን አገልግሎት መጀመሩን፣
  4. በአመስተረዳም፣ ዋሽንግተንና ለንደን የሚገኙትን ስቱዲዮዎች የሚሰጡትን አገልግሎት ለማሳደግ የሚያስፈልገውን እቅድ አውጥቶ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን፣
  5. በሃገር ውስጥ የሚገኙትን የዜና ወኪሎች ሁለንተናዊ አቅም ለማሳደግ እቅድ አውጥቶ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን፣
  6. ድረ-ገጹን ለአገልግሎት አጠቃቀም እንዲያመች (USER FRIENDLY) እና ዘመናዊ ይዘት እንዲኖረው ከፍተኛ ጥረት በማድረግ በአገልግሎት ላይ ማዋሉን፣

አመላክቶ  ነበር።

ከዚያም በኋላ ተከታታይነት ባለው መንገድ በወሰደው፤ ሥርጭቱን የማስፋት እና አገልግሎቱን የማጠናከር፤ ተግባር በአሁኑ ጊዜ ኢሳት፤

  1. የአጭር ሞገድ የሬድዮ ስርጭቱ ላይ የሚደርሰውን አፈና ለመቋቋም ያስችለው ዘንድ አምስት አማራጭ ሞገዶችን በመጨመር፤ በአጠቃላይ በሰባት ሞገዶች፤ ማለት፥ 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz እና 15390kHz ወደ ኢትዮጵያ ማስተላለፍ ጀምሯል።  በዚህም ኢሳት፣ በቀን አንድ ሰዓት፤ ማለት፥ ከምሽቱ 2 እስከ 3 ሰዓት፤  በሰባቱም ሞገዶች እንደሚያሰራጭ ለማያውቁ እንዲያሳውቁ ጥሪ ያደርጋል።
  2. በድረገጹ www.ethsat.com የሚተላለፈውን የ24 ሰዓት የቴሌቪዠን ስርጭት በማንኛውም ኮምፒዩተር  ላይ ሊሰራ  በሚችለው የፍላሽ (FLASH) ስርጭት ለመተካት ወራት የፈጀውን ቅድመ ዝግጅቱን በማጠናቀቅ አገልግሎት  ላይ አውሏል።
  3. የ24 ሰዓት የሳተላይት ሬድዮ ስርጭት በቀጥታ ወደ ኢትዮጵያ በሳተላይት ቴሌቪዥን ማሰራጨቱን ለማጠናከር ተጨማሪ  ሳተላይት  የተከራየ ሲሆን፤ ይህም አዲስ የሳተላይት ሬድዮ በ Atlantic Bird 7 Satellite, KU Band, 7.2 Degrees West, Transponder: C8, Downlink Frequency: 11354 Vertical, Symbol Rate = 27500, FEC = 5/6 ይገኛል።

 

እነዚህ ዘርፈ ብዙ ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች በአግባቡ ለማከናወንም ሆነ በተከታታይነት እያጠናከሩ ለመቀጠል እንዲቻል የኢሳት የፋይናንስ አቅም በተጠናከረና አስተማማኝ መሠረት ላይ መቆም ይገባዋል። በዚህ ረገድ፣ ይህ በጥር ወር እንዲጀምር የታሰበው ዓለም-አቅፍ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዘመቻ በታቀደው መሠረት ለማከናወን ከፍተኛ ጥረት  ማድረጉ አማራጭ የሌለው ተግባር ነው።

 

በገንዘብ ድጋፍ ማሰባሰቢያው ዘመቻ ከተጠቀሱት አማራጭ የድጋፍ አይነቶች ውስጥ፤ ከላይ ለተጠቀሱት እንቅስቃሴዎች የሚያስፈልገውን ወጭ ለመሸፈን፣ ለአሰባሰብም ሆነ ለአጠቃቀም አስተማማኝና አመቺ ሆኖ የተገኘው፤ በየወሩ ከባንክዎ ወደ ኢሳት ባንክ በሚተላለፈው የቋሚ ክፍያ የሚደረገው ድጋፍ ነው። ይኸውም፣ በየወሩ ከባንክዎ ወደ ኢሳት ባንክ የሚተላለፈው የሂሳብ መጠን አሁን ኢሳት ባለበት የገንዘብ ወጪ አኳያ በትንሹ ከሃያ የአሜሪካ ዶላር ($20) ጀምሮ ሊሆን ይገባዋል። አቅምዎ የሚፈቅድ ከሆነ በወር ከተቀመጠው ዝቅተኛ ክፍያ ($20) በላይ በቋሚነት ኢሳትን ሊደግፉ ይችላሉ። ይህንንም ለማድረግ በቀጥታ በኢሳት ድረ-ገጽ ላይ ለዚሁ አመቺነት ተብሎ የተዘጋጀው ይህ ገጽ  http://ethsat.com/Main/esat_recurring_monthly_donation.html  በመጎብኘት ዛሬውኑ መተግበር ይችላሉ።

 

በተለያዩ ምክንያቶች ከባንካችሁ በቀጥታ በየወሩ ለኢሳት ድጋፍ ማድረግ ለማትችሉ ወገኖች በዚሁ በዓለም-አቀፍ ደረጃ በሚደረገው የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዘመቻ ላይ ያቀረብናቸውን $100/£100/€100 ልዩ ቲኬት የምትችሉትን ያህል ብዛት በመግዛት ወገናዊ ግዴታችሁን መወጣት ትችላላችሁ። የቲኬት አቅርቦትን በተመለከተ የአካባቢዎን የኢሳት ተወካይ ለማግኘት እንዲችሉ በኢሳት ድረ ገጽ www.ethsat.com ላይ የተቀመጠውን የስልክ መረጃ መጠቀም ይችላሉ።

 

በመጨረሻም፣ ኢሳት በዚህ አጭር እድሜው ብዙ ፈተናዎች አጋጥመውታል። እነዚህ ፈተናዎች ቀላላ አልነበሩም። ፈተናዎቹን ለመወጣት ባደረገው ጥረት በቂ ተመክሮ አዳብሯል። ኢሳት ከፈተናዎቹ ያዳበረውን ልምድ በመጠቀምና ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በመሆን ምንም ዓይነት ፈተና ማለፍ እንደሚቻል ሙሉ እምነት አለው። ለዚህም ነው ኢሳት የእያንዳንዱን ሃገርና ወገን ወዳድ ድጋፍ በመጠየቅ ለዕርሶም ጥሪውን የሚያቀርበው።

 

የኢሳት የነጻነት መንፈስ ለዘላለም ይኑር!!!
ኢሳትን መደገፍ ባስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያለችውን ሀገራችንና ወገናችንን መታደግ ነው!!!

የኢሳት አስተዳደር
www.ethsat.com